2 ተሰሎንቄ 3:6-18
(2 ተሰሎንቄ 3:6-18) አሁንም፥ ወንድሞች ሆይ፥ ከእኛ እንደ ተቀበለው ወግ ሳይሆን ያለ ሥርዓት ከሚሄድ ወንድም ሁሉ ራሳችሁን እንድትለዩ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዛችኋለን። እኛን ልትመስሉ እንዴት እንደሚገባ ራሳችሁ ታውቃላችሁና፤ በእናንተ ዘንድ ያለ ሥርዓት አልሄድንምና፤ የማንንም እንጀራ በከንቱ አልበላንም። ነገር ግን ከእናንተ በአንዱ ስንኳ እንዳንከብድበት ሌሊትና ቀን በድካምና በድካም ሠራን፤ እኛን እንድትከተሉ ራሳችንን ለእናንተ ምሳሌ እንሆን ዘንድ እንጂ ኃይል ስለሌለን አይደለም። ከእናንተ ጋር ሳለን መሥራት የማይወድ አይብላ ብለን አዘናችሁ ነበርና። በመካከላችሁ ያለ ሥርዓት የሚሄዱ እንዳሉ ሰምተናልና፤ ከቶ ሳይሠሩ ነገር ግን በሥራ የተጠመዱ ናቸው። እንደነዚህ ያሉትንም በጸጥታ ሠርተው የራሳቸውን እንጀራ ይበሉ ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እናዛቸዋለን እንመክራቸውማለን። እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ በመልካም ሥራ አትታክቱ። በዚህ መልእክት ለተጻፈው ቃላችን የማይታዘዝ ማንም ቢኖር፥ ያንን አስተውለው ያፍርም ዘንድ ከእርሱ ጋር አትተባበሩ። ነገር ግን እንደ ወንድም ምከሩት እንጂ እንደ ጠላት አትቁጠሩት። የሰላምም ጌታ ራሱ ሁልጊዜ በሁሉ መንገድ ሰላምን ይስጣችሁ። ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን። በገዛ እጄ ያለው የጳውሎስ ሰላምታ ይህ የመልእክቱ ሁሉ ምልክት ነው፤ እንዲሁ እጽፋለሁ። የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን። ኣሜን። ጳውሎስ እያዘዘ...